የበቀለ ጨቅላ.. ስመኘው ሞኝ ተላላ!

Poems

ብያሬድ ሕሉፍ


ዘመድ
 የለ ፈጥኖ ደራሽ

የሚያበረታታ 

በተዘጋ ቤት ፍርስራሽ

ውሀ የለ ሚበላ ቁራሽ

መኖር ግድ ሆኖ ሥጋ ለባሽ:

ቀን እስኪያፍ እስኪመሻሸ:

ባለኣደራ ኣትክልትማሙሽ

ባፈራ እንዴት ደስ ባለኝ : ደም መላሽ::

 

ይሄው ለዓመታት ስመኝ ሳይታክተኝ ሳይደክመኝ ምን እለ ቢያድለኝ ለተከፍው ልቤማፅናኛ ደብዳቤ:

ጌታ ልጅ ቢስጠኝከሚታመን ጏድ ከሚወደኝ ኣለሁ ባይ ሲከፋኝ:

 ደስታዬም ተካፍይ : ልጅ ካለም ተንከባካይ:: በዓለም ከዚህ በላይ ምን ኣለ ሌላ ንዋይ::

 

ታድያ ስኖር ስንገላታ ስወጣ ስወርድ በርካታ ካሳስብኝ ሁኔታመለስ ብሎ ጌታ

ተስፋ እንዳልቆርጥ እንድበረታስመፕው ውሎ ያደረ:

ባለውለታ ባልጌታ ወረወረመህፀኔም ቆጠቆጠ መሀን ሁኖ ኣልቀረየበቀለ ልጅምስመፕው ተባለ:: አድጎምእጅ ስነዘረ:

ለተከፋው ሁሉ አጥቶት ለነበረ ውሀ ምግብ ላቅብ ኣለ

ጉልበት እስከቻለ::

 

መሳቅ ኣይሉት ገደብ የለሽ ሳቀ ፍፁም በደስታ ልቤ ፈነደቀፍትሕ መሬት ላይ ፀደቀ::

 

በዚያው ልክም ምቀኛ ፈለቀ ከወሀ ጥም ድሀን ላላቀቀ ወነጄለው ጉሮሮው እንዳደረቀእርር ድብን ብሎምበንዴት ደቀቀ:

ግራ ቅኝም ተቻኮለ

ልጄን ሊያጠፋ ምን ግዜ ኸጀለ::

 

ታድያ በጠማማ አእምሮ ኣምባጏሮ ጭሮ

ንፁሃን ገደለ ልጄንም ጨምሮ:: ላያልቅ የኔ እሮሮ!

ወይ ዘንድሮ!

 መቼ ያልቃል ተነግሮ

ቀማኛ ካልተመቸው ኑሮ

አቅመ ቢሱን ስባብሮ

ልበ ቁኑን አጭበርብሮ

ሁሉ እንዲጠፋ ተበነቃቅሮ ይራራጥ ጀመረ በአስተክሮየአህያዋን ምሳሌ ተክትሎ:

እኔ ከሞትኩኝ በኃላ

ስርዶ አይብቀል እንኻን የሚበላ“,

የበቀለ ጨቅላ..

ስመኘው ሞኝ ተላላ!

 

 

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *